ባለማወቅ ሳይሆን በድፍረት
ፈጽመው ትልቅ ኀጢአት
አዳምና ሔዋን ሲወጡ ከዚያ ቤት
ከመልካሙ ኤድን ገነት፤
ከበዛበት መዘዙ
ወደ’ንግዳ ዓለም ሲጓዙ
እየፈሩና እየቸሩ
ከቀድሞ ቤታቸው ሲባረሩ፤
በደልን ተሸክመው
ኃፍረትንም ለብሰው
ደስታን ተሰናብተው
የሕይወትን ዛፍ ትተው፤
እንዳይቀርቡ ወደሱ ጋ
የገነት በር ከኋላቸው ተዘጋ።
ከወጡ በኋላ ከዚያ ሥፍራ
ሔዋን አዝና ስትል ወዮ
ድምጿ ተሰማ ቀራንዮ።
(ተዛማጅ ትርጉም፤ ግርማ ዳምጤ ሀብተየስ፤ ቁርስ፤ ገጽ 160)










